ኢዮብ

ብዙ ነገሮችን እንዳስብና እንዳሰላስል ከሚያደርጉኝ መፅሀፎች ውስጥ አንዱ የኢዮብ መፅሀፍ ነው። ብዙ ጊዜ የኢዮብን መፅሀፍ ስናስብ ቶሎ ብሎ ትዝ የሚለን፥ ኢዮብ ያለፈባቸው በጣም ከባባድ ፈተናዎች ናቸው። መቼም የእግዚአብሄር ፀጋ የማያሳልፈው ነገር የለም እንጂ ማናችንም ብንሆን፥ ኢዮብ ያለፈባቸውን ፈተናዎች እንኳን ልናልፍባቸው፥ ለማሰብ እንኳን የሚከብዱን ናቸው።

ከትዳር በፊት ማወቅ ያሉብኝ ነገሮች

ዛሬ በጣም ደክሞኛል። ምን የመሰለ ሰርግ ላይ ውዬ አሁን ቅርብ ጊዜ ነው ወደ ቤቴ የገባሁት። አቤት ሙሽሮቹ እንዴት እንደሚያምሩ! ሚዜዎቹስ ብትሉ፥ የተነገረው የእግዚአብሄር ቃል፥ የቃልኪዳን ስነስርዓቱ፣ የሰርጉ አዳራሽ ደግሞ ማማሩ! አምልኮውንማ አጠይቁኝ፥ በቃ ቀውጢ ነበር። እስኪያልበን ድረስ መዝለላችን፥ አምልኮ የሚለውን ቃል ባይተካውም፥ ያው እየዘለልን ዘምረናል። ምናለበት ግን የእሁድ እሁድ የቤተክርስቲያን አምልኮአችንም እንዲህ ቢመስል! ማለት፥ ተፈቶ ሲያመልክ አይተነው የማናውቀው ሰው ሁሉ ሰርግ ላይ ሲፈታ እናየዋለን።

ትምህርት ቤት

አንድ የቅርብ ጉዋደኛዬ በህክምና ፊልድ ውስጥ የመሆንና በዚህ የስራ ዘርፍ የማገልገል ከፍተኛ የሆነ ፍላጎት ስለነበራት፥ በነርሲንግ ፕሮግራም ውስጥ ገብታ ለሁለት አመታቶች በትጋት ትምህርትዋን ትከታተል ነበር። የቅርብ ወዳጄ በመሆንዋ፥ በተገናኘንባቸው ጊዜያቶች ሁሉ የትምህርትዋን ሁኔታ ታጫውተኝ ነበር።

ችላ ያልነው ጠላታችን

አንዳንድ ጊዜ ስፀልይ፥ ስዘምር፥ መፅሀፍ ቅዱሴን ሳነብ በጣም መንፈሳዊ እንደሆንኩ ብቻ ሳይሆን መልአክ እንደሆንኩኝም ነው የሚሰማኝ። በግራና በቀኜ ያሉትን ክንፎቼን ፈልጌ ሳላበቃ፥ መልሼ ራሴን የማልጠብቀው ቦታ ላይ አገኘዋለሁ።

ልቤ

ዛሬ ቀኑ ፀሀያማና ደስ የሚል ነው። እኔም ከሰዎች ጋር አንድ አስፈላጊ ቀጠሮ ስላለኝ ወደዛ ለመሄድ እየተዘጋጀሁ ነው። መዘነጥ አይበላችሁ! ፏ ብያለሁ! የክት ልብሴን ለባብሼ፥ ፀጉሬን አስተካክዬ፥ ሽቶዬን ተቀባብቼ ከጨረስኩ በኋላ፥ ከመውጣቴ በፊት ለመጨረሻ ጊዜ ራሴን በመስታወት ማየት ስለነበረብኝ ወደ መስታወቱ ጋር ጠጋ ብዬ ራሴን ማየት ጀመርኩ። እዛው እንደቆምኩ ጥቂትም ሳይቆይ ነው ሀሳቦች በልቤ መምጣት የጀመሩት።

ደውል

አንዳንድ ጊዜ ቤቴ ውስጥ ቡና ሳፈላ፥ ጣሪያ ላይ ያለችው የእሳት አደጋ ደውል የቡናውን ጭስ ሰምታ ጩኸትዋን ታቀልጠዋለች። በሩን ከፍቼ የቡናውን ጭስ ካላስወጣሁትማ፥ እልህ ይይዛታል መሰለኝ ብሶባት ነው ቁጭ የሚለው። ለነገሩ እሷ ምን ታርግ? ስራዋን እኮ በአግባቡ እየሰራች ነው።

ሩጫ

በልጅነቴ በጣም ከምወዳቸው ነገሮች አንዱ ሩጫ ነበር። በአጭሩ፥ ቆመን እናውራ ከምትሉኝ እየሮጥን እናውራ ብትሉኝ ይቀለኝ ነበር። አንዳንዴማ ማዘር ሱቅ ስትልከኝ፥ ለመሮጥ ከመቸኮሌ የተነሳ የምገዛውን ነገር በሙሉ ተናግራ እስክትጨርስ ለመስማት የሚሆን ትእግስት አልነበረኝም። እሷ ተናግራ ሳትጨርስ እኔ ሮጬ ሱቁ ጋር ደርሻለሁ። ግዢ ያለችኝን ነገሮች በትክክል ስላልሰማሁ ተመልሼ ስመጣ፥ ማዘር እዛው ቦታ ጋር ቆማ እየጠበቀችኝ ነው።

መታዘዝ

ዛሬ በጠዋት አስፈላጊ የሆነ ቀጠሮ ስለነበረኝ በጊዜ ነበር ለመሄድ የተነሳሁት። መሄድ የነበረብኝ ቦታ እኔ ከምኖርበት ሰፈር ራቅ ያለ ስለነበር፥ የቦታውን አድራሻ ወስጄ ስልኬን ወደዛ ቦታ እንድትመራኝ በትህትና ጠየኳት። እግዚአብሄር ይስጣት ለደቂቃ እንኳን ሳታንገራግር ነው እሺ ብላ የምፈልግበት ቦታ ያደረሰችኝ። ዝም ብዬ ግን አልደረስኩም። ወደምፈልገው ቦታ ለመድረስ የእሷን ምሪት ተማምኜ አርጊ ያለችኝን ሁሉ ነው ያደረኩት።

How do I know the will of God in my romantic relationship?

Relationships are fun! It is nice to have someone to lean on and share romantic love with. I believe most of us have at least experienced what it feels like being in a relationship and having someone to love. As fun as they are, as a Christian, it is crucial to take the time to know how to navigate through a relationship with the word of God.

የተፈጠርኩበትን ዓላማ የማውቀው እንዴት ነው?

ብዙ ሰው በህይወቱ መጨረሻ ቁጭቶች ይኖሩታል። ይሄንን ነገር ማድረግ ነበረብኝ ወይንም ማድረግ አልነበረብኝም የሚላቸው ነገሮች ይበዛሉ። በመፅሀፍ ቅዱስ ውስጥ በእድሜው መጨረሻ ህይወቱን ዞር ብሎ አይቶ የእርካታና የደስታ ንግግር ከተናገሩ ሰዎች መካከል አንዱ ጳውሎስ ነው።

አላማ

አንዳንድ ጊዜ የሰው ልጆችን ህይወት ቆም ብላችሁ ስታስቡት በተመሳሳይ ነገር የተሞላ ነው:: ሰው ይወለዳል, ያድጋል, ይማራል, ያገባል, ይወልዳል, ከቻለ ቤት እና መኪና ይገዛል, ከዚያ ያረጅና ይሞታል:: የሚያረጀውም እግዚእብሄር እድሜና ጤና ከሰጠው ብቻ ነው:: የሰው ልጅ ህይወቱ ከዚህ ተመሳሳይ ድግግሞሽ አያመልጥም:: እግዚአብሄር የጥበብን መንፈስ የሞላበት ሰው ጠቢቡ ሰለሞን ህይወትንና የሰው ልጆችን እንቅስቃሴ ሁሉ አስተውሎ ከተመለከተ በሗላ ያለው ነገር ይገርመኛል:: “... ከንቱ ከንቱ ሁሉ ከንቱ ነው...”

Purpose of Singleness

Have you heard people say, “She is so beautiful. How come she is not taken? or “He is handsome and has got it all together. Why is he still single?”. I'm pretty sure we have all said it or heard other people say it. The statement isn’t wrong, yet it can slowly lead people to conclude that there must be something wrong with staying single.