All tagged Meaningful life

አንዲቷ  ልመና

ከሌሊቶች ውስጥ በአንዱ ሌሊት ነው እግዚአብሄር ለንጉስ ሰለሞን በራእይ ተገልጦ ምን እንድሰጥህ ለምነኝ ያለው። ለእኛ ለሰዎች መለመን ብዙም የሚያስደስተን ነገር አይደለም። ምክኒያቱ ደግሞ የበዛውን ጊዜ ለመስጠት ስንነሳ፥ ከራሳችን የሚጎልብን ነገር ስላለ ነው።

ዘላለም

ዛሬ ስራ ቦታዬ በስራ ብዛት የተጨናነቀ ነበር። የስራዬ ባህሪ ከተለያዩ ሰዎች ጋር የሚያገናኘኝና ከሰዎች ጋር እንዳወራና እንድጫወት እድል የሚሰጠኝ ነው። በተፈጥሮዬ ከሰዎች ጋር መግባባት ለኔ ከባድ የሚባል ስራ ስላልሆነ፣ ስራዬን እወደዋለሁ። በስራዬ መካከል በምወስዳቸው የእረፍት ሰአቶች ግን የምፈልገው አንድ ነገር ብቻ ነው። ጸጥታ።

የተፈጠርኩበትን ዓላማ የማውቀው እንዴት ነው?

ብዙ ሰው በህይወቱ መጨረሻ ቁጭቶች ይኖሩታል። ይሄንን ነገር ማድረግ ነበረብኝ ወይንም ማድረግ አልነበረብኝም የሚላቸው ነገሮች ይበዛሉ። በመፅሀፍ ቅዱስ ውስጥ በእድሜው መጨረሻ ህይወቱን ዞር ብሎ አይቶ የእርካታና የደስታ ንግግር ከተናገሩ ሰዎች መካከል አንዱ ጳውሎስ ነው።