All tagged Living the will of God

አንዲቷ  ልመና

ከሌሊቶች ውስጥ በአንዱ ሌሊት ነው እግዚአብሄር ለንጉስ ሰለሞን በራእይ ተገልጦ ምን እንድሰጥህ ለምነኝ ያለው። ለእኛ ለሰዎች መለመን ብዙም የሚያስደስተን ነገር አይደለም። ምክኒያቱ ደግሞ የበዛውን ጊዜ ለመስጠት ስንነሳ፥ ከራሳችን የሚጎልብን ነገር ስላለ ነው።

ስኬት

ስኬት ስለሚለው ቃል ስናስብ መቼም ሁላችንም ልብ ውስጥ የሚመጡ ይሄን ይሄን ባሳካ ብለን በልባችን ውስጥ የምናስባቸው፣ የአጭርና የረጅም ጊዜ ስኬቶች ይኖሩናል። ከዚያም በተጨማሪ ደግሞ በአካባቢያችን ላይ የምናውቃቸው ወይንም በsocial media ገጾቻችን እነሱ እንኳን ሳያውቁን እኛ የምናውቃቸውና የምንከተላቸው፣ በየቀኑ የሚያወጡትን ፎቶዎች እያየን የስኬት ምሳሌዎች ያረግናቸው ሰዎችም ይኖራሉ። ስኬት ለሁሉም ሰው የተለያየ ትርጉም ያለውና በህይወት ዋጋ ከምንሰጣቸው ነገሮች ጋር የተያያዘ ነገር ነው።

ዘላለም

ዛሬ ስራ ቦታዬ በስራ ብዛት የተጨናነቀ ነበር። የስራዬ ባህሪ ከተለያዩ ሰዎች ጋር የሚያገናኘኝና ከሰዎች ጋር እንዳወራና እንድጫወት እድል የሚሰጠኝ ነው። በተፈጥሮዬ ከሰዎች ጋር መግባባት ለኔ ከባድ የሚባል ስራ ስላልሆነ፣ ስራዬን እወደዋለሁ። በስራዬ መካከል በምወስዳቸው የእረፍት ሰአቶች ግን የምፈልገው አንድ ነገር ብቻ ነው። ጸጥታ።