All tagged Spiritual growth

መታዘዝ

ዛሬ በጠዋት አስፈላጊ የሆነ ቀጠሮ ስለነበረኝ በጊዜ ነበር ለመሄድ የተነሳሁት። መሄድ የነበረብኝ ቦታ እኔ ከምኖርበት ሰፈር ራቅ ያለ ስለነበር፥ የቦታውን አድራሻ ወስጄ ስልኬን ወደዛ ቦታ እንድትመራኝ በትህትና ጠየኳት። እግዚአብሄር ይስጣት ለደቂቃ እንኳን ሳታንገራግር ነው እሺ ብላ የምፈልግበት ቦታ ያደረሰችኝ። ዝም ብዬ ግን አልደረስኩም። ወደምፈልገው ቦታ ለመድረስ የእሷን ምሪት ተማምኜ አርጊ ያለችኝን ሁሉ ነው ያደረኩት።