በልጅነቴ በጣም ከምወዳቸው ነገሮች አንዱ ሩጫ ነበር። በአጭሩ፥ ቆመን እናውራ ከምትሉኝ እየሮጥን እናውራ ብትሉኝ ይቀለኝ ነበር። አንዳንዴማ ማዘር ሱቅ ስትልከኝ፥ ለመሮጥ ከመቸኮሌ የተነሳ የምገዛውን ነገር በሙሉ ተናግራ እስክትጨርስ ለመስማት የሚሆን ትእግስት አልነበረኝም። እሷ ተናግራ ሳትጨርስ እኔ ሮጬ ሱቁ ጋር ደርሻለሁ። ግዢ ያለችኝን ነገሮች በትክክል ስላልሰማሁ ተመልሼ ስመጣ፥ ማዘር እዛው ቦታ ጋር ቆማ እየጠበቀችኝ ነው።