All tagged Learning from the Israelites

መማር

ሰሞኑን የኢያሱን መጽሀፍ በፍቅር ነው እያነበብኩት ያለሁት። መጽሀፉን በአንድ ቃል ግለጪው ተብዬ ብጠየቅ መውጣትና መውረስ ብዬ እገልጸዋለሁ። ለነገሩ ገና መጽሀፉስ ሲጀምር እግዚአብሄር ለኢያሱ መጥቶ ለአባቶቻቸው አሰጣችሀዋለሁ ብዬ የማልሁላቸውን ምድር ለዚህ ህዝብ ታወርሳለህና ጽና አይዞህ። ብሎ በእሱ ህይወት ሊሰራ ያሰበውን የማውረስ አገልግሎት አይደል እንዴ ቀድሞስ ቢሆን የተናገረው።