አንዳንድ ጊዜ የሰው ልጆችን ህይወት ቆም ብላችሁ ስታስቡት በተመሳሳይ ነገር የተሞላ ነው:: ሰው ይወለዳል, ያድጋል, ይማራል, ያገባል, ይወልዳል, ከቻለ ቤት እና መኪና ይገዛል, ከዚያ ያረጅና ይሞታል:: የሚያረጀውም እግዚእብሄር እድሜና ጤና ከሰጠው ብቻ ነው:: የሰው ልጅ ህይወቱ ከዚህ ተመሳሳይ ድግግሞሽ አያመልጥም:: እግዚአብሄር የጥበብን መንፈስ የሞላበት ሰው ጠቢቡ ሰለሞን ህይወትንና የሰው ልጆችን እንቅስቃሴ ሁሉ አስተውሎ ከተመለከተ በሗላ ያለው ነገር ይገርመኛል:: “... ከንቱ ከንቱ ሁሉ ከንቱ ነው...”